የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ9 ቢሊየን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ባለፉት ስድስት ወራት ከታክስ በፊት 9 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ኃይለ ሚካኤልን ጨምሮ የተቋሙ ሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ምልከታ እያደረጉ ነው።

በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የቢዝነስና ዴቨሎፕመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃኔ ገብረእግዚአብሔር የተቋሙን የስድስት ወራት አፈፃፀም አቅርበዋል።

በዚህም የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ በማሳለጥ በኩል የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑን አንስተዋል።

ከዕለት ፍጆታ ዕቃዎችና ሸቀጦች ጀምሮ ልዩ ልዩ የፋብሪካ ውጤቶችን፣ አነስተኛና ትላልቅ ማሽነሪዎችን፣ ተሽከርካሪዎችን፣ የኮንስትራክሽን ግብዓቶችንና የተለያዩ ጭነቶችን በባህርና በየብስ ትራንስፖርት በማጓጓዝ የተሟላ የሎጅስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ እንዳለም ተናግረዋል።

ባለፉት ስድስት ወራት 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ቶን የገቢና የወጪ ንግድ ጭነት አገልግሎት መስጠቱን ጠቅሰዋል።

ከሚሰጣቸው አገልግሎቶችም በግማሽ ዓመቱ 44 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት አቅዶ ከ46 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ገልፀዋል።

ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ99 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

በዚህም ተቋሙ ከታክስ በፊት 6 ቢሊየን ብር ለማትረፍ አቅዶ 9 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱን ጠቅሰዋል።

ትርፉ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ188 በመቶ ብልጫ እንዳለውም ነው ያብራሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025