የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

መንግስት ሁሉን አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት በትኩረት እየሰራ ነው

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ሁሉን አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር ለሴቶች እና ወጣቶች የዲጂታል ፋይናንሻል አገልግሎት ስልጠና ሰጥቷል።


ስልጠናው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀ እና የዲጂታል አቅምን ማጎልበት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን (ዶ/ር) መንግስት በኢትዮጵያ አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ለዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

የሴቶችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገትን ማፋጠን እንደሚገባም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቅሰው ሴቶች በዲጂታል ኢኮኖሚ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተዋል።

ስልጠናው በዲጂታል ባንክ አገልግሎትና በዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት እድሎችና ተግዳሮቶች፣ ሞባይል ባንኪንግ፣ የቴሌ ብር አገልግሎት ለሴቶች እና ሌሎች ተጓዳኝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025