
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ሁሉን አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር ለሴቶች እና ወጣቶች የዲጂታል ፋይናንሻል አገልግሎት ስልጠና ሰጥቷል።

ስልጠናው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀ እና የዲጂታል አቅምን ማጎልበት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን (ዶ/ር) መንግስት በኢትዮጵያ አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ለዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
የሴቶችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገትን ማፋጠን እንደሚገባም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቅሰው ሴቶች በዲጂታል ኢኮኖሚ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተዋል።
ስልጠናው በዲጂታል ባንክ አገልግሎትና በዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት እድሎችና ተግዳሮቶች፣ ሞባይል ባንኪንግ፣ የቴሌ ብር አገልግሎት ለሴቶች እና ሌሎች ተጓዳኝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025