የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በክልሉ በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር የታቀፉ ወገኖች በዘላቂነት እንዲቋቋሙ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው ነው</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ የካቲት26/2017 (ኢዜአ) ፡-በትግራይ ክልል በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር የታቀፉ ወገኖች በዘላቂነት እንዲቋቋሙ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለጸ።

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አልማዝ ገብረፃዲቅ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ በአምስት ከተሞች የምግብ ዋስትና ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ተግባራዊ እየተደረገ ነው።

በዚህም ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን በልማታዊ ሴፍቲኔት በማቀፍ ሰርተው እንዲለወጡ የማድረግ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በመጀመሪያው ዙር የከተሞች የምግብ ዋስትና ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በአምስት ከተሞች ከ34 ሺህ 600 በላይ ዜጎች መታቀፋቸውን አስታውሰው በግማሽ በጀት ዓመቱ ሰርተው ለሚከፈላቸውና በቀጥታ ለሚደገፉ ወገኖች ከፌደራል መንግስት የተላከ 14 ሚሊዮን ብር ስራ ላይ መዋሉን ገልፀዋል።


በሁለተኛው ዙር የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚዎችም ሰርተው በመለወጥ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እንዲችሉ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ከመርሃ ግብሩ ተጠቃሚዎች መካከል በመቀሌ ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ መሰረት ገብረ እግዚአብሔር፤ በወር ሰርተው ከሚከፈላቸው ወርሃዊ ደሞዝ 20 በመቶውን በመቆጠብ ህይወታቸውን በዘላቂነት ለማሻሻል ጥረት እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል።

ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ ወጣት ዛይድ አለምሰገድ፤ በአረንጓዴ ልማት ላይ በመሰማራት በተለይ የተተከሉ ችግኞች እና የውበት ስፍራዎች በመንከባከብ በወር አምስት ሺህ ብር እንደምታገኝ ተናግራለች።


በመርሃ ግብሩ ሰርተን መለወጥ እንደምንችል ጥሩ አጋጣሚ በመሆኑ ለስኬት እየተጋን እንገኛለን ብላለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025