
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2017 ( ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ጃንግዙ የኢኮኖሚና የንግድ ትብብር ኮንፈረንስ የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ እንደሚያግዝ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮምሽነር ዝናብ ይርጋ ኮንፍረንሱ የኢትዮጵያና የቻይና ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ የንግድ፣የኢኮኖሚና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሻግር ጠቁመዋል።
ምክትል ኮምሽነሩ አክለውም ይህን መሰል ዝግጅት የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ ያግዛል ብለዋል።
በማኑፋክቸሪንግና በአይ ሲ ቲ ግዙፍ ስም ያላቸው የጆንግዙ የንግድ ልኡካን በኢትዮጵያ መዋዕለንዋያቸውን ቢያፈሱ ኮምሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል ።
በወቅቱ በሀገሪቱ ስላሉ የኢንቨስትመንት እድሎች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በኮንፈረንሱ ከ200 በላይ የጃንግዙና የኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብ መሳተፋቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025