አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ ጥገና መከናወኑን የክልሉ መንገድና ሎጂስቲክስ ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በክልሉ የመንገድ ተደራሽነትን የሚያሰፉና ህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚሳድጉ የመንገድ ልማትና ጥገና ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ገልጿል።
በኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በሚዘጋጀው 'ጉሚ በልበሎሚ' የውይይት መድረክ በመንገድ ጥገና እና የፕሮጀክቶች መጓተትና ጥራት ችግሮች እንዳሉ ተነስቷል።
የቢሮ ሃላፊ ጫላ አብዲ(ኢንጂነር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በሁሉም የክልሉ ዞኖች የመንገድ ግንባታና ጥገና ሥራዎች እየተከናወነ ነው።
በክልሉ ቀበሌን ከቀበሌ፣ ወረዳን ከወረዳ እንዲሁም ከዋና ዋና መንገዶች ጋር የሚያገናኙ የመንገድ ግንባታና ጥገና መከናወኑን አንስተዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት የመንገድ ፈንድ በማቋቋም 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ የመጠገኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በተያዘው በጀት ዓመትም የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት አዲስ የመንገድ ዝርጋታና ጥገና ላይ ሰፊ ስራዎችን እየተሰራ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል በፌደራልና በክልሉ መንግስት መንገድ ፈንድ በኩል 7 ሺህ 44 ኪሎ ሜትር መንገድ ከባድና ቀላል ጥገና ለማከናወን በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን አስታውቀዋል።
ቢሮው የጥገና አቅሙን ለማጎልበት ባለፉት ዓመታት ግዙፍ የጥገና ማሽኖችን መግዛቱን አስታውሰዋል።
"ጉሚ በልበሎሚ" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ የህዝብ ጥያቄ በመሰብሰብና ሰፊ ጥናት በማካሄድ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ምላሽ የሚጠይቅበት የውይይት መድረክ ነው።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025