የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በክልሉ በሁለት ዓመታት ውስጥ 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ ተጠግኗል</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ ጥገና መከናወኑን የክልሉ መንገድና ሎጂስቲክስ ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በክልሉ የመንገድ ተደራሽነትን የሚያሰፉና ህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚሳድጉ የመንገድ ልማትና ጥገና ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ገልጿል።

በኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በሚዘጋጀው 'ጉሚ በልበሎሚ' የውይይት መድረክ በመንገድ ጥገና እና የፕሮጀክቶች መጓተትና ጥራት ችግሮች እንዳሉ ተነስቷል።

የቢሮ ሃላፊ ጫላ አብዲ(ኢንጂነር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በሁሉም የክልሉ ዞኖች የመንገድ ግንባታና ጥገና ሥራዎች እየተከናወነ ነው።

በክልሉ ቀበሌን ከቀበሌ፣ ወረዳን ከወረዳ እንዲሁም ከዋና ዋና መንገዶች ጋር የሚያገናኙ የመንገድ ግንባታና ጥገና መከናወኑን አንስተዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት የመንገድ ፈንድ በማቋቋም 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ የመጠገኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት አዲስ የመንገድ ዝርጋታና ጥገና ላይ ሰፊ ስራዎችን እየተሰራ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል በፌደራልና በክልሉ መንግስት መንገድ ፈንድ በኩል 7 ሺህ 44 ኪሎ ሜትር መንገድ ከባድና ቀላል ጥገና ለማከናወን በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን አስታውቀዋል።

ቢሮው የጥገና አቅሙን ለማጎልበት ባለፉት ዓመታት ግዙፍ የጥገና ማሽኖችን መግዛቱን አስታውሰዋል።

"ጉሚ በልበሎሚ" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ የህዝብ ጥያቄ በመሰብሰብና ሰፊ ጥናት በማካሄድ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ምላሽ የሚጠይቅበት የውይይት መድረክ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025