የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በክልሉ ከመኸር እርሻ ከ44 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከመኸር እርሻ ከ44 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ።

በበጋ ወቅት መደበኛ የመስኖ ልማት ሥራም በክልሉ ከ146 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱም ተመላክቷል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) የክልሉን የአስፈፃሚ ተቋማት የስድስት ወራት ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ዛሬ ለክልሉ ምክር ቤት አቅርበዋል።

በሪፖርቱም በክልሉ የመኸር እርሻ ወቅት ከ557 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን ገልጽዋል።

በዚህም ከ44 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።


የክልሉን የግብርና አቅም አሟጦ በመጠቀም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማሳካትና ዘርፉ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉለህ አስተዋጽኦ እንዲኖረው በቅንጅት መሰራቱን ተናግረዋል።

ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብአትና ለቴክኖሎጂ አቅርቦትና አጠቃቀም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ድጋፍና ክትትል ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው፣ በተሰራው ሥራ የተገኘው ውጤት ገበያን ለማረጋጋት እያገዘ ነው ብለዋል።

በክልሉ ግብርናን ለማሳደግ የተጀመረው ቅንጅታዊ ጥረት በአዳዲስ እሳቤዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።

አሁን ላይ በበጋ ወቅት በሚከናወን መደበኛ መስኖ ልማት ከ146 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መገባቱንም አንስተዋል።


ክልሉ ያለውን የገቢ አማራጭ አሟጦ በመሰብሰብ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመፍታት በተደረገ እንቅስቃሴም ከ6 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቁመው፣ ይህም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 39 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።

በግማሽ በጀት ዓመቱ በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ከ215 ሺህ በላይ ዜጎችን በጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏልም ነው ያሉት።

በትምህርት ዘርፍ የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል የሚያችል የትምህርት ቤቶች ደረጃ የማሻሻል ሥራን ጨምሮ የግብአትና የመምህራን አቅም ግንባታ ሥራዎች መከናወናቸውንም ተናግረዋል።

በጤናው ዘርፍም በሽታን መከላከልን መሰረት ባደረገ መልኩ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው፣ በተለይ የሕክምና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በግማሽ በጀት ዓመቱ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች በክልሉ አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውቀዋል።

የምክር ቤቱ አባላትም በሪፖርቱ ላይ ያላቸውን ጥያቄና አስተያየት በማቅረብ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025