የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶችን መደገፍ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ንግድ መድን ኤጀንሲ የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን መደገፍ የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የአፍሪካ የንግድ መድን ኤጀንሲ ተወካዮች ፈርመውታል።

በአፍሪካ ቀዳሚው የፓን አፍሪካ የንግድ እና የመድን ኢንቨስትመንት የሚሰኘው የአፍሪካ የንግድ መድን ኤጀንሲ በታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ስጋት እንዳያጋጥም የፋይናንስ ድጋፍ የሚያመቻች ተቋም ነው።

ስምምነቱም በኤጀንሲው ቀጣናዊ የድጋፍ ማዕቀፍ ውስጥ የኢትዮጵያ ታዳሽ ሃይል ልማት ላይ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ያግዛል ተብሏል።

በተመሳሳይ ስምምነቱ በኢትዮጵያና በኤጀንሲው መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በሃይል አቅርቦት ዘርፍ ለሚስተዋሉ ቁልፍ የፋይናንስ ችግሮች ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳ ተጠቁሟል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በአጋርነት ስምምነቱ ለአልሚዎች ወቅታዊ ክፍያ ለመክፈል፣ የፋይናንስ ኪሳራ ለመቀነስና የሃያል ሽያጭ ስምምነቶችን ለማጠናከርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተዓማኒነትን ለማጎልበት እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።

መሰል የአጋርነት ጥረቶች በታዳሽ ሃይል ኢንቨስትመንት ምቹ ከባቢ እንደሚፈጥር መናገራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኤጀንሲው ዋና ስራ አስፈጻሚ ማኑኤል ሙሴ በበኩላቸው ስምምነቱ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ስጋትን መቀነስ ብቻ ሳይሆን በኃይል መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንትን ያሳድጋል ብለዋል።

ይህም የኢትዮጵያን የታዳሽ ሃይል አቅም የሚያሳድግ እና በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን የሚያጎለብት መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ንግድ መድን ኤጀንሲ ጋር በታዳሽ ሃይል መሰረተ ልማት ድጋፍ የተፈራረመች 11ኛዋ ሀገር ሆናለች።

ከዚህም በፊት ቤኒን፣ ቡሩንዲ፣ ኮቲዲዩቫር፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ቶጎ፣ ኡጋንዳና ዛምቢያ በታዳሽ ሃይል ድጋፍ ማዕቀፍ የተፈራረሙ አባል ሀገራት ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025