
አዲስ አበባ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(ተመድ) የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስር ከፈተ።
ጥምረቱ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) እና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ይፋ አድርጓል።
የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ለዘላቂነት ልማት እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮችን ለመፍታት በዓለም ዙሪያ ያሉ የፈጠራ ልሂቃንና የቴክኒክ ባለሙያዎች ያሰባስባል።
በአዲስ አበባ የተከፈተው የጥምረቱ ቢሮም የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን ለፖሊሲ አውጭዎች ግብዓት የሚሆኑ ሳይንሳዊ መፍትሔዎችን ያቀርባል ተብሏል።
የጥምረቱ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጀፍሪ ሳክስ እንዳሉት፣ የጥምረቱ ተቀዳሚ ዓላማ በዓለም ላይ ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና እና ማህበራዊ ፍትህ ማስፈን ነው።
መንግስታትን መደገፍ ዘላቂ የልማት ግቦችን ማሳካት በመሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መፍትሔ በማፈላለግ ላይ ሊያተኩሩ ይገባል ብለዋል።
በአዲስ አበባ በይፋ የተከፈተው የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ቢሮም አፍሪካ ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መስራት የዓለም ስልጣኔ ፈርቀዳጅ መሆኗን የገለጹት ጀፍሪ ሳክስ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑንም ተረድቻለሁ ብለዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) የዘላቂ የልማት ግቦች የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ን ከግብ ለማድረስ ቁልፍ መንገድ መሆኑን ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጥናትና ምርምር የላቀ አገልግሎት እንዳለው የገለጹት ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረቱ ተጨማሪ አቅም ስለሚሆነው በትብብር እንሰራለን ለዚህ ደግሞ ቁርጠኛ ነን ብለዋል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025