
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባ ከተማን ከሸገር ከተማ የሚያገናኙ አዳዲስ እና ነባር መንገዶች ግንባታ እና ማስፋፊያ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።
የመንገዶቹን ግንባታ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች እየጎበኙ ይገኛሉ።
የሸገር ከተማን የሚያቋርጡ እና በሁሉም አቅጣጫ ወደ አዲስ አበባ የሚያስገቡ መንገዶች ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ያለባቸው በመሆኑ መንገዶቹን ለማሻሻል የጥናት ስራዎች መከናወናቸው ተገልጿል፡፡
በዚህም በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ችግሮችን በመፍታት የትራፊክ ፍሰቱን ለማስተካከል ደረጃቸውን የጠበቁ መንገዶች ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው ተብሏል።

የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በግንባታ ላይ የሚገኙ አዲስ አበባ - ሆለታ መንገድ ማሻሻያ ፕሮጀከት፣ ከእንጦጦ ማርያም ጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል እና ከስፔስ ኦብዘርቫቶሪ ጫካ መንደር ፕሮጀክት መንገዶች ግንባታን ጎብኝተዋል፡፡
የመንገዶቹ ግንባታ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲጠናቀቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ገልጿል።
አዲስ አበባን ከሸገር ከተማ ከሚያገናኙ መንገዶች መካከል የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ - ጂዳ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑንና ግንባታው በቅርቡ እንደሚጀመርም ተጠቁሟል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025