የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የአልጄሪያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንት መስኮች እንደሰማሩ ጥሪ ቀረበ</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017 (ኢዜአ):- የአልጄሪያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሙሃመድ ጠየቁ።

አራተኛው ዓለም አቀፍ የግንባታ፣ ኮንስትራክሽን እና የከተማ ልማት ኤግዚቢሽን በአልጄሪያ ምስራቃዊ ክፍል በምትገኘው የአነባ ግዛት ዋና መቀመጫ አነባ ከተማ ተካሄዷል።

በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሙሃመድ በኤግዚቢሽኑ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያና አልጀሪያ በዲፕሎማሲ ረገድ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው አገራት መሆናቸውን አውስተዋል።

የአልጄሪያ ባለሀብቶች በአዲስ አበባ በቀጣይ በሚካሄደው የሁለቱን አገራት የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ጋብዘዋል።

ጉብኝቱ ለድርጅቶቹና ለባለሀብቶቹ በኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች ለማየት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርላቸው አመልክተዋል።

አምባሳደር ሙክታር ከኤግዚቢሽኑ ጎን ለጎን በተለያዩ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና ቁሳቁሶች ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከተሰማሩ የአልጄሪያ ድርጅቶች እና ባለሀብቶች ጋር ተወያይተዋል።

አምባሳደሩ በውይይቱ ስለ ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት እድሎች ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ሚሲዮኑ ለባለሀብቶቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በኤግዚቢሽኑ ላይ በርካታ ኩባንያዎች ከመደበኛ እስከ ስማርት መኖሪያ ቤቶች እና ሪል ስቴቶች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶች እና ግብዓቶች ለእይታ ማቅረባቸውን በአልጀርስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025