
አዲስ አበባ፤ጥር13/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከጂቡቲ ጋር ያላት የጸና ትብብርና የመሠረተ ልማት ትስስር ለጋራ ዕድገትና ለአዳዲስ ዕድሎች ምቹ መደላድል የሚፈጥር ነው ሲሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
ሚኒስትሩ፥ ዛሬ በኢትዮ-ሎጅስቲክስ የዘርፍ ማኅበራት በተዘጋጀው የቢዝነስ ማጎልበቻ ኮንፈረንስ ላይ ተገኝተዋል።
በዚህም ከጂቡቲ ጋር ያለውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነት አስፈላጊነት እና የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣናው የንግድ እድሎችን ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠናል ብለዋል።
ከጂቡቲ ጋር ያለን የጸና ትብብርና የመሠረተ ልማት ትስስር ለጋራ ዕድገትና ለአዳዲስ ዕድሎች ምቹ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቁመዋል።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ተግዳሮቶችን በማስወገድ ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ስምምነት ጋር የሚስማማና አስተማማኝ የትብብር ማዕቀፍን እውን ለማድረግ በትጋት እየሰራ ነው መሆኑንም ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግና ግብርናን መሰረት ያደረገና ብዝሃነት ያለውን የውጭ ንግድ ለማስፋት ለሚሰራው ስራ ጂቡቲ ስትራቴጂክ አጋር መሆኗን ነው የገለጹት።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025