
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት መደረጉን የኦቪድ ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ ታደሰ ገለጹ።
የኦቪድ ሆልዲንግ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር እስከ 2030 ለማሳካት ያለመውን የአምስት ዓመት ሥትራቴጂክ ዕቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅዱም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ አጋርነትና ትብብር፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ እንዲሁም ብቃትና ለደንበኞች ትኩረት መስጠት የሚሉ መርሆዎችን የያዘ ነው።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው በመርሃ-ግብሩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለደንበኞቻችን የገባነውን ቃል ኪዳን እና ለተሻለች ኢትዮጵያ እውን መሆን በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን በይፋ ባስጀመሩበት ማግስት ስትራቴጂው ይፋ መደረጉም መልካም አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ በመንግሥት አነሳሽነት የተጀመረው የቤት ልማት አጋርነት ለግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።
በመሆኑም የግሉ ዘርፍ መንግሥት የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም ለኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግና ቁልፍ ሚናውን ሊጫወት ይገባል ብለዋል።
መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆየው የቤት አቅርቦት ችግሮች በጥናት መለየታቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም በዘርፉ ላይ የታዩትን ሳንካዎች እንደ ችግር ከማየት ይልቅ ወደ መልካም አጋጣሚነት ለመቀየር ቆርጠን ተነስተናል ብለዋል።
በዚህም የኦቪድ ሆልዲንግ 2030 ስትራቴጂ እውን ለማድረግ በመሰረታዊ ችግሮች ላይ የሚወሰዱ የመፍትሔ ርምጃዎች ላይ አተኩረን እንሰራለን ነው ያሉት፡፡
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025