
ጅማ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት አምስት ወራት 617 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ ገለጹ።
በጅማ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የፋይናንስ፣ የፕላንና ገቢዎች የምክክር መድረክ ዛሬ በገቢ አሰባሰብ ላይ አተኩሮ ውይይት አድርጓል።

በዚሁ ጊዜ የገቢዎች ሚኒስትሯ ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ፤ ባለፉት አምስት ወራት ለመሰብሰብ የታቀደው 648 ቢሊዮን ብር መሆኑን ገልጸው 617 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ይህም ለመሰብሰብ ከታቀደው 95 በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።
የበጀት ዓመቱን እቅድ ለማሳካትም የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት የደረሰኝ ማጭበርበርንና የታክስ ስወራን መከላከል ላይ በትኩረት እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በተጨማሪም የግብር ከፋዩን ግንዛቤ ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎችን ማጠናከር፣ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማገዝም ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ነው ያሉት።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025