የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በመኽር አዝመራ በተካሄደ በርበሬ ልማት ከ720 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጭሮ ፣ጥቅምት 26/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በመኽር ወቅቱ ከለማው በርበሬ ከ720 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በጽህፈት ቤቱ የቡና ሻይ እና ቅመማ ቅመም ልማት ቡድን መሪ አቶ ኦሉማ በዳኔ እንዳሉት በዞኑ በመኸር አዝመራ በ15 ወረዳዎች 34 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በርበሬ ለምቷል።

በዞኑ ምርቱ በስፋት በሚካሄድባቸው የሀዊ ጉዲና ፤ ጭሮ፤ ዳሮ ለቡ፤ ገመቺስ ፤ሀብሮ ፤ኦዳ ቡልቱም እና ቦኬ ወረዳዎች የምርት ስብሰባ እየተካሄደ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

በዚህ ዓመት ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው ምርት ካለፈው ዓመት ከአስር ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ እንደሚኖረው ነው ያመለከቱት፡፡

በዞኑ የበርበሬ አኒሼቲቭን ለማሳካት አርሶአደሩ ልማቱን በክላስተር በማልማት በጋራ እንዲሳተፍ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡

አርሶአደሮች ለምርት ጥበቃና እንክብካቤ ትኩረት እንዲሰጡ በተደረገው ድጋፍና ክትትል በሄክታር የምርታማነት መጠኑን ከ16 ኩንታል ወደ 20 ኩንታል ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል፡፡

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን 15 ወረዳዎች እየተካሄደ ባለው የበርበሬ ልማት ከ55 ሺህ በላይ አርሶአደሮች እየተሳተፉ መሆኑም ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025