🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት የወሰደባትን 30 ዓመታት ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ ሌላ 30 ዓመታት አያስፈልጋትም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ በተካሀደበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት የወሰደባትን 30 ዓመታት ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ ሌላ 30 ዓመታት አያስፈልጋትም ብለዋል።
የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ(ጂኦግራፊያዊ) እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ ያህል የወሰደ ትግል እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሀገሪቱ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ነው ያሉት።
ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም ሲሉም በአጽንኦት ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ካቢኔ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩት መሆኑን ጠቁመው፤ ጥያቄው ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው እንደሆነም ነው የገለጹት።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025