የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በደሴ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ተጀመረ

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በደሴ ከተማ አስተዳደር ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለየዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል።

በመጀመሪያው ዙር ከ1 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት በማከናወን ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ተመልክቷል።


የከተማው አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ እንደገለጹት፣ የበጀት ዓመቱ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ተገብቷል።

በዚህም የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄ እና የከተማውን የእድገትና አሻጋሪ እቅድ መነሻ በማድረግ በተያዘው በጀት ዓመት ከ20 በላይ ፕሮጀክቶች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።

በዚህም ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የበጀት ዓመቱ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ዛሬ በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል።

ከኮሪደር ልማቱ በተጨማሪ የአንድ ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ፣ የሥራ እድል መፍጠሪያ ሼዶች፣ የጤናና የትምህርት ቤቶች ማስፋፊያ ከፕሮጀክቶቹ መካካል እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት እንዲሰሩ ሕብረተሰቡ ሰላሙን በማፅናት የጀመረውን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል።


የደሴ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አንዷለም እሸቱ በበኩላቸው፤ ፕሮጀከቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት እንዲጠናቀቁ የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።

ለዚህም አስፈላጊው ግብዓትና ፕሮጀክቶችን መስራት የሚያስችል ዝግጅት ተደርጎ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ዛሬ መጀመሩን አረጋግጠዋል።


በፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፤ ከተማ አስተዳደሩ ሕብረተሰቡን በማስተባበር ጭምር ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ልማት እየሰራ መሆኑን በማንሳት መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ዛሬ የተጀመሩ ልማቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ የድርሻቸውን እንደሚወጡም አስታውቀዋል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025