የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በኢትዮጵያ 100 ከተሞችን ተደራሽ የሚያደርግ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ተግባራዊ ሊደረግ ነው

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ 100 ከተሞችን ተደራሽ የሚያደርግ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ፕሮጀክት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡

ኢንስቲትዩቱ ጎንደር ከተማን የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ፕሮጀክት የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ዛሬ ተፈራርሟል፡፡


የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሐይ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያን ታላላቅ ከተሞች ዘመኑን የዋጀ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡

ኢንስቲትዩቱ በ10 ዓመት ውስጥ 100 ከተሞችን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ስራ መግባቱን ጠቁመው በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ የክልል ከተሞችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል፡


በአማራ ክልል የደብረ ብርሃንና የኮምቦልቻ ከተሞች የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተው፤ በደሴና ወልዲያም ፕሮጀክቱን ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡

የከተሞች የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ የሚያደርጉትን የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያፋጥን ከመሆኑም በላይ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ ለሆኑ ከተሞች የላቀ አበርክቶ አለው፡፡


ዲጂታል የአድራሻ ስርዓት መኖሪያ ቤቶችን፣ መንገዶችንና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያሉበትን መገኛ ቦታ ርቀትና አቅጣጫ በቀላሉ ለማመልከት የሚያስችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንደሆነም አብራርተዋል፡፡

ዲጂታል የአድራሻ ስርዓት ለከተሞች ፈጣን እድገትና ለውጥ ቁልፍ የቴክኖሎጂ መሳሪያ ነው ያሉት የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው፡፡


የጎንደር ከተማ ሰባት ታላላቅና ታዋቂ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች እንዳሏት ጠቅሰው፤ እነዚህን የቱሪዝም የመስህብ ሀብቶች በማስተዋወቅ ቱሪስቶች ስፍራዎቹን በቀላሉ እንዲጎበኙ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ቴክኖሎጂ ነው ብለዋል፡፡

ከተማ አስተዳደሩ ለፕሮጀክቱ ተፈጻሚነት ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅርበት የሚሰራ ሲሆን በመጪው ጥር ወር በከተማው በድምቀት ለሚከበረው የጥምቀት በዓል ቴክኖሎጂውን ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የኢንስቲትዩቱ የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025