🔇Unmute
አዳማ ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በበጀት ዓመቱ 11 ሚሊዮን የዓሣ ጫጩቶችን በማሰራጨት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሣ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት የሌማት ትሩፋት ፕሮግራምን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ስርዓተ ምግብን እውን ለማድረግ ወደ ተግባር ተገብቷል።
በዚህም ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች አንዱ የዓሣ እርባታ ሥራ መሆኑን ገልጸው፣ ሥራው በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ ሐይቆች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ 11 ሚሊዮን የዓሣ ጫጩቶችን በማሰራጨት 320 ሺህ ቶን አሣ ለማምረት ግብ መጣሉን ተናግረዋል።

ዕቅዱን ለማሳካት የአሣ ጫጩት ማስፋፊያ ማዕከላት በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች እየተገነቡ መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ሙቀትና ቅዝቃዜን የሚቆጣጠር ዘመናዊ የአሣ ጫጩት ማመላለሻ ማሽኖች ለክልሎች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።
የንጋት ሐይቅን ጨምሮ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሐይቆች እንዲሁም በአርሶ አደሩ ቀዬ በሚሰሩ ኩሬዎች የአሣ ጫጩቶች የማስገባት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ከሐይቆችና ኩሬዎች አሣን በአግባቡ ለመሰብሰብም ዘመናዊ የዓሣ ማስገሪያ መረቦችና ጀልባዎች ለክልሎች እንዲሰራጩ መደረጉን ነው ፍቅሩ (ዶ/ር) የገለጹት።
በዚህም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትና እና ሥርዓተ ምግብን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025