🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 5/2018(ኢዜአ)፡- 219 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ጨምሮ በአምሥት የገበያ ማዕከላት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦት በበቂ ሁኔታ የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።
የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ንግድ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አሸናፊ ብርሃኑ እንዳሉት፤ 219 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ጨምሮ በአምሥት የገበያ ማዕከላት የዋጋ ንረትን ያረጋጋ ግብይት እየተከናወነ ነው።
ለእነዚህ ገበያዎችና ማዕከላት የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርት በበቂ ሁኔታ ከሥር ሥር እየቀረበ መሆኑንም ለኢዜአ አረጋግጠዋል።
በየሳምንቱ እየወጣ ባለው የዋጋ ተመን መሠረት ግብይት እንደሚከናወንም አስረድተዋል።
ከሌሎች ነጻ ገበያዎች አንጻር በቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በአምሥቱ ገበያ ማዕከላት በአማካይ ከ20 በመቶ በላይ ቅናሽ ተደርጎ እንደሚሸጥም ተናግረዋል።
በሁሉም የመዲናዋ ወረዳዎች የቅዳሜና እሁድ ገበያ መኖሩን ጠቅሰው፤ ከፍላጎት ማደግ አንጻር በቀጣይ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን የማስፋት ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን አመላክተዋል።
በዚህም መሰረት አንድ የቅዳሜና እሁድ ገበያ ስፍራ ባላቸው ወረዳዎች ተጨማሪ እንዲኖር ይደረጋል ብለዋል።
እነዚህ የገበያ አማራጮች በተቀመጠው አሠራር መፈጸማቸውን የሚከታተሉ ሱፐር ቫይዘሮች መመደባቸውን እና 1 ሺህ 216 የግብይት ተቆጣጣሪዎች በስምሪት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ሕገ ወጥ ድርጊት ሲፈጽሙ የተገኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያ ሻጮች ከትስስር ውጭ እንደሚደረጉ እና በሕግም ተጠያቂ እንደሚሆኑ አስገንዝበዋል።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025