🔇Unmute
ወልዲያ፤ጥቅምት 2/2018(ኢዜአ)፦የወልድያ ከተማ የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ግንባታ በመገባደድ ላይ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ንጉስ ዝናቡ፤ በከተማዋ የመጀመሪያው ምእራፍ የኮሪደር ልማት ከአዳጎ አደባባይ በመነሳት እስከ ጎንደር በር ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ አፈፃፀሙ ከ96 በመቶ በላይ መድረሱን አንስተው፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተመርቆ ለአገልግሎት የሚበቃ ይሆናል ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የአስፋልት መንገድ ግንባታና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ አረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ መሆኑን አንስተው፥ በጥራትና በፍጥነት መከናወኑንም ተናግረዋል።
በዚህም ከ300 በላይ ለሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን አንስተው፥ ከተማዋን የማልማት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ፍስሃ መንግስቴ እና ወይዘሮ አልማዝ አያሌው፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ውብና ለኑሮ ምቹ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ልማቱ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎች፣ ለባለሃብቶችና ሌሎች አገልግሎት ሰጭዎች ምቹ አካባቢን የፈጠረ በመሆኑ የሚደነቅ ስራ ነው ብለዋል።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025