
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1 /2017 (ኢዜአ)፦ ህፃናትና ወጣቶች በአካል እና በአዕምሮ ብቁ ሆነው እንዲያድጉ የከተማ አስተዳደሩ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን ግንባታ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዛሬ ማለዳ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መሪ ሎቄ 40/60 ኮንዶሚኒየም አካባቢና በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን ዛሬ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ ከተማ አስተዳደሩ 15ሺህ 960 ፕሮጀክቶችን ገንብቶ ማጠናቀቁን ተናግረዋል።
ግንባታቸው ከተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል 122 የስፖርት ማዘውተሪያ እና 1ሺህ 155 የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች መሆናቸውን ተናግረው፤ ይህም ህፃናትና ወጣቶች በአካልና በአዕምሮ ብቁ ሆነው እንዲያድጉ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አስተዳደሩ የሚገነባቸው ፕሮጀክቶች ህፃናትና ወጣቶችን ታሳቢ ያደረጉ እንደሆኑም ከንቲባዋ ተናግረዋል።
የአካባቢው ነዋሪዎች መሰረተ ልማቶቹን በአግባቡ በመጠቀም ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ እንዳለበትም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025