የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአደጋ ጊዜ ለሰብዓዊ ድጋፍ ደራሽ ለመሆን የዝግጁነት አቅምን ማጠናከር ይገባል

Jul 3, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦በአደጋ ጊዜ ለሰብዓዊ ድጋፍ ደራሽ ለመሆን የዝግጁነት አቅምን ማጠናከር እንደሚገባ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ገለጹ።

''ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነትና ለተሟላ ክብር'' በሚል መሪ ሃሳብ ሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የአመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የተገኙት መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር)፤በአደጋ ጊዜ ለሰብዓዊ ድጋፍ ደራሽ ለመሆን የዝግጁነት አቅምን ማጠናከርና ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም በየደረጃው ያለው አመራር በቂ ግንዛቤ ኖሮች ለተግባራዊነቱ በቅንጅት መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን የሚያስችላት እምቅ አቅምና ሰፊ እድሎች ያሏት መሆኑን ያነሱት ዶክተር መሪሁን፤ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ ተስፋ ሰጭ የልማት ጥረቶችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

በግብርናም ይሁን በሌሎች ሴክተሮች ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ጥረቶች ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን አንስተው፥ በምርታማነት ከእርዳታ ጠባቂነት መውጣት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በክልሉ ባለፈዉ የበልግ ወቅት ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ በተዘጋጁ መጋዝኖች ምርት የተከማቸባቸው መሆኑን ገልጸው፥በቀጣይም መጠናከር እንዳለበት አንስተዋል።


የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋንታ ጋምአ፤ በክልሉ የሚፈጠሩ አደጋዎችን በራስ አቅም ምላሽ መስጠትና መቋቋም የሚያስችል ዝግጁነት እንዲኖር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በሌማት ትሩፋት፣በበጋ መስኖ ስንዴና በሌሎችም የግብርና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የምርታማነት አቅሞች እየተፈጠሩ መሆኑንም አንስተዋል።

በመድረኩ የክልል፣የዞን፣ የከተማ እና የወረዳ አስተዳደር አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025