የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፈላጊ ደንበኞች በፍጥነት ምላሽ የሚያገኙበት አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ነው

Jul 1, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ ፤ሰኔ 21/2017 (ኢዜአ) ፡-የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፈላጊ ደንበኞች በፍጥነት ምላሽ የሚያገኙበት አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሲዳማ ሪጅን አስታወቀ።

በኢትዮጵያ ኢሌክትሪክ አገልግሎት የሲዳማ ሪጅን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማግኘት የሚጠይቁ አዲስ ደንበኞችን በ24 ሰዓት ውስጥ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል “ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን” የተሰኘ አሰራር ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡

በአገልግሎቱ ሁሉንም ሂደት ጨርሰው ለሚመጡ ደንበኞች በአንድ ቀን ቆጣሪ በማስገባት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያገኙበትን ፈጣንና ቀልጣፋ አሰራር ተግባራዊ እያደረገ ነው።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የሲዳማ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ፤ አገልግሎቱ የአዲስ ደንበኞችን ጥያቄ በፍጥነት ምላሽ ለመስጠት በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት ባለፉት 11 ወራት ብቻ 11 ሺህ 23 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።


በሲዳማ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደንበኞች ተሳትፎና ቁልፍ ደንበኞች ኃላፊ ትዝታ አስናቀ፤ በዘመቻ እየተከናወነ ባለው አሰራር በርካቶች ተጠቃሚ ስለመሆናቸው አንስተዋል።

በተቋሙ ስታንዳርድ መሠረት አንድ ደንበኛ በ10 ቀናት ውስጥ ለጠየቀው አገልግሎት ምላሽ በመስጠት ላይ እንገኛለን ያሉት ኃላፊዋ ስኬታማ ስራ መሆኑንም ተናግረዋል።

አገልግሎቱን ካገኙ ደንበኞች መካከል የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው አቶ ዜና ደመቀ፤ አሰራሩ እንግልት የሌለውና ሁላችንንም ያስደሰተ ነው ብለዋል።

ከዚህ በፊት ለጥያቄው ምላሽ ለማግኘት የተለያዩ ምክንያቶች እንደነበሩ አንስተው አሁን ላይ ችግሩ ተፈትቶ የተቀላጠፈ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።


የብረታ ብረት ባለሙያ የሆነው ወጣት አሸናፊ ተስፋዬ፤ ለጠየቀው አገልግሎት በአንድ ቀን ቆጣሪ አግኝቶ የኃይል ተጠቃሚ በመሆኑ እየሰራ ባለው የብረታ-ብረት ስራ ውጤታማ መሆኑን ተናግሯል።

አገልግሎቱ ባለፉት 11 ወራት የሥነ-ምግባር ጥሰት ታይቶባቸዋል ባላቸው 48 ባለሙያዎቹ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን መውሰዱም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025