የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የበኩሉን ሚና እየተወጣ ይገኛል

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ለማጠናከር የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ "ጥራት ያለው ትምህርት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን በሚመለከት ውይይት ተካሂዷል፡፡


ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳ አካል የሆነውን የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን የማረጋገጥ ግብን ለማሳካት በርካታ ተግባራትን ማከናወኗ በመድረኩ ተገልጿል፡፡


ከዚህ አኳያ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ለማስቀጠልና የገጠሙ ተግዳሮቶችን በመፍታት ግቡን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ምክክር ተደርጓል።


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው ለዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት የሚጠበቅበትን እያበረከተ ነው፡፡


በዚህም ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን እንዲሁም የፈጠራ ሥራና የማህበረሰብ አገልግሎት በማከናወን ለግቡ ስኬት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


ዩኒቨርሲቲው ግቦቹን በስትራቴጂክ ዕቅዱ በማካተት ለስኬቱ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ ዘላቂ የልማት ግቦችን ውጤታማ ለማድረግ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡


የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ጀይሉ ኡመር (ዶ/ር) በበኩላቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት ትልቅ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡


ለዚህም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥና ተደራሽነትን በማስፋት ለግቡ ስኬት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡


በዩኒቨርሲቲው የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዲን የቆየዓለም ደሴ (ዶ/ር) ፥ የትምህርትን ዘላቂ የልማት ግብ ለማሳካት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና፣ ትምህርትን በፋይናንስ መደገፍና ወቅታዊ አተገባበርን በተመለከተ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት እንደተካሄደባቸው ገልጸዋል፡፡


ዩኒቨርሲቲው ለዘላቂ የልማት ግቡ ስኬት የተለያዩ ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025