የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ ተግባራዊ የሚደረጉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የአካባቢ ብክለት መከላከልን ማዕከል ሊያደርጉ ይገባል

Jun 10, 2025

IDOPRESS

ወራቤ፤ ሰኔ 2/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተግባራዊ የሚደረጉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የአካባቢን ብክለት መከላከልን ማዕከል እንዲያደርጉ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡

ቢሮው ከክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በክልሉ የሚገኙ ፋብሪካዎችና የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢ ብክለት ተፅዕኖን ለመከላከል ያለመ የምክክር መድረክ በወራቤ ከተማ አካሂዷል፡፡


የቢሮው ኃላፊ አብርሃም መጫ በወቅቱ እንዳሉት ቢሮው የተፈጥሮ ሀብትን በመንከባከብ ፅዱ አካባቢን ለመፍጠር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡

በዚህም የክልሉ ከተሞችን ፅዱና የአካባቢ ብክለትን ታሳቢ ያደረጉ ተግባራትን በማከናወን የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ ሀገር በቀል ችግኞችን እየተከሉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም በክልሉ በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ አካላት የአካባቢን ብክለት መከላከልን መሰረት ያደረጉ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል፡፡


የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደምሰው ባቾሬ በበኩላቸው በአካባቢ ብክለት ምክንያት የሚከሰትን ሁለንተናዊ ጫና ለመከላከል በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ለማረም ቢሮው በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡

በዚህም ለአዳዲስ ኢንቨስትመንቶች የአካባቢ ብክለትን መከላከል በሚያስችል መልኩ በክላስተር መሬት የማዘጋጀት ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል፡፡


በዞኑ የሚከናወን የትኛውም የልማት ስራ የአካባቢንና የማህበረሰቡን ጤና ማስጠበቅን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን ትኩረት መሰጠቱን የገለጹት ደግሞ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዘይኔ ቢልካ ናቸው፡፡

ዞኑን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ በተሰጠው ትኩረት በርካታ ባለሀብቶች ዘርፉን እየተቀላቀሉ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


የደስታ ጋርመንት ዋና ስራ አስኪያጅ ያሬድ ወልዴ በበኩላቸው ከፋብሪካው የሚወገዱ ተረፈ ምርቶች አካባቢን እንዳይበክሉ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና በተለያየ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች የተሳተፉ ሲሆን የፅዳት ዘመቻና የችግኝ ተከላ መርሐ ግብርም አከናውነዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025