
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የብሪክስ አባል ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ጥሪ አቀረቡ።
የብሪክስ የትራንስፖርት ሚኒስትሮች ስብሰባ በብራዚል መዲና ብራዚሊያ ተካሄዷል።
ኢትዮጵያ በስብሰባው ላይ በትራንስፖርት ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ለውጦች አቅርባለች።
አዲስ ግዙፍ አየር ማረፊያ ግንባታ፣ የአየር ማረፊያዎች ማስፋፊያ እና የደረቅ ወደቦችን ጨምሮ የትራንስፖርት ዘርፉን የማዘመን ግብ ያላቸው ከፍተኛ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለማሳያነት ቀርበዋል።
በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል የመሆን ግብ እንዳላት ገልጸዋል።
አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት ከተቀረው ዓለም ጋር በማስተሳሰር እድገትን፣ትስስር እና ዘላቂነትን እውን ለማድረግ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
አምባሳደሩ የብሪክስ ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩም ጥሪ አቅርበዋል።
ሚኒስትሮቹ ስብሰባውን ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ያወጡ ሲሆን ትራንስፖርት የእድገት እና ዘላቂ ልማት አሳላጭ እንደሆነ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025