የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የብሪክስ ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር ማጠናከር ይገባቸዋል - አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ

May 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የብሪክስ አባል ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ጥሪ አቀረቡ።


የብሪክስ የትራንስፖርት ሚኒስትሮች ስብሰባ በብራዚል መዲና ብራዚሊያ ተካሄዷል።


ኢትዮጵያ በስብሰባው ላይ በትራንስፖርት ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ለውጦች አቅርባለች።


አዲስ ግዙፍ አየር ማረፊያ ግንባታ፣ የአየር ማረፊያዎች ማስፋፊያ እና የደረቅ ወደቦችን ጨምሮ የትራንስፖርት ዘርፉን የማዘመን ግብ ያላቸው ከፍተኛ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለማሳያነት ቀርበዋል።


በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል የመሆን ግብ እንዳላት ገልጸዋል።


አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት ከተቀረው ዓለም ጋር በማስተሳሰር እድገትን፣ትስስር እና ዘላቂነትን እውን ለማድረግ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።


አምባሳደሩ የብሪክስ ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩም ጥሪ አቅርበዋል።


ሚኒስትሮቹ ስብሰባውን ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ያወጡ ሲሆን ትራንስፖርት የእድገት እና ዘላቂ ልማት አሳላጭ እንደሆነ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025