የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት መስክ ያላቸውን ጠንካራ ትብብር ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል - አምባሳደር ጁንግ ካንግ

May 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላቸውን ጠንካራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ጁንግ ካንግ ገለጹ።

የኮሪያ ሪፐብሊክ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ መስዋዕትነት የተከፈለበትና በደም የተገመደ ጭምር ነው፡፡

በዚህም የኮሪያ ሪፐብሊክ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት 74 ዓመታትን አስቆጥሮ ዛሬ ላይ የደረሰ ሲሆን በጦርነቱ ኢትዮጵያ የነበራት ተሳትፎ ኮሪያ ሪፐብሊክ አሁን ላይ ለተጎናጸፈችው ነፃነት ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡

በተለይ ባለፉት 20 ዓመታት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ጁንግ ካንግ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ሁለቱ ሀገራት በንግድና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ጠንካራ ትብብር የበለጠ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል።

ኢትዮጵያ ለኮሪያ ሪፐብሊክ ነጻነት የከፈለችው መስዋዕትነት የኮሪያ ሪፐብሊክ ህዝብና መንግስት ሁል ጊዜም እውቅና የሚሰጠውና ምስጋና የሚቸረው ታሪክ ነው ብለዋል።

ሁለቱ ሀገራት ያለችውን ረጅም ዘመን ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር በጋራ ፍላጎት ላይ ተመስርተው እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል።

ለአብነትም በባህል ልውውጥ፣ በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በጤናና መሰረተ ልማት ግንባታ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

በተጨማሪም በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍም እንዲሁ ያላቸውን ትብብር በማጎልበት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶታል ነው ያሉት።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ረገድ የምታደርገው ጠንካራ ተሳትፎ የሚደነቅ እና ክብር የሚሰጠው መሆኑንም አምባሳደሩ አክለዋል።

74ኛ ዓመቱን ያስቆጠረውን የኮሪያ ሪፐብሊክ ሰላም ማስከበር ተልዕኮን ጨምሮ ኢትዮጵያ በኮንጎ፣ ሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ሱማሊያ፣ ብሩንዲ እና ደቡብ ሱዳን ያከናወነችው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ተጠቃሽ ነው።

ኢትዮጰያና ኮሪያ ሪፐብሊክ ዘመናትን የተሻገረና በመስዕዋትነት የተሳሰረ ወዳጅነት እንዲመሰርቱ አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025