የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በትንሳዔ በዓል የኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል

Apr 21, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በትንሳዔ በዓል ሰሞን የኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በአገልግሎቱ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የኔትወርክ መሰረተ ልማት ኃላፊ አቶ ደጀኔ ጥጋቡ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ከበዓሉ ጋር ተያይዞ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።

በበዓሉ ወቅት የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት ከኤሌክትሪክ መስመር ጋር የሚነካኩ የዛፍ ቅርንጫፎችን የማስተካከል፣ የአገልግሎቱ ሰራተኞችን ግንዛቤ ማሳደግና የመስመሮችን ደህንነት የማየት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

መስሪያ ቤቱ በበዓሉ ወቅት በድንገት ለሚያጋጥም የኃይል መቋረጥ ችግርም ፈጣን ምላሽና የጥገና አገልግሎት የሚሰጥ ኮማንድ ፖስት ማቋቋሙንም ገልጸዋል።

የኤሌክትሪክ መቋረጥ ሲያጋጥም ደንበኞች ችግሩን በፍጥነት ማሳወቅ እንዲችሉም ተጨማሪ የስልክ መስመር መዘርጋቱን ተናግረዋል።

አቶ ደጀኔ አክለውም፥ ህብረተሰቡ በበዓሉ ወቅት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲጠቀም ኃይልን በሚቆጥብና የአጠቃቀም መደራረብ ችግር በማይፈጥር መልኩ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025