
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ)፦ ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት ሊቆጠብ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታወቀ።
ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት አጠራጣሪ መልዕክት ሲያገኝ ለተቋሙ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች ያስተላለፈው የጥንቃቄ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
የጥንቃቄ መልዕክት ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች!
የኢንተርኔት አጠቃቀም በየቀኑ እየጨመረ በሄደበት በዚህ ዘመን፣ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ስጋቶችም እየተስፋፉ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በቅርቡ በርካታ አደገኛ የኢንተርኔት አድራሻዎችን (URLs) መርምሮ፣ እነዚህ አድራሻዎች ለሀገራችን የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በይበልጥ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች አካዉንቶችን በመንጠቅ ከፍተኛ ስጋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ አረጋግጧል። ከተለያዩ አካላት በቴሌግራም የሚደርሱን ሊንኮች በርካታ አደጋዎችን የሚይዙ ሲሆን የሚከተሉት አደጋዎች በዋናነት ይገኙበታል፡

የግል መረጃ መጠለፍ:- እንደ የባንክ መለያ ወይም የይለፍ ቃል ያሉ መረጃዎችን መሰረቅ፤

የማልዌር ስርጭት:- ስልኮችን ወይም ኮምፒውተሮችን የሚጎዱ ቫይረሶች፤

ማጭበርበሪያ:- ተጠቃሚዎችን በሀሰተኛ ተስፋዎች (እንደ ውርርድ ወይም ኢንቨስትመንት) መታለል፤
በመሆኑም ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ እያሳሰብን፤ ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና በፍጹም ልንከፍታቸዉ ከማይገቡ ሊንኮች መካከል የሚከተሉት ከታች በምስሉ ያሰፈርናቸዉ ይገኙበታል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በቴሌግራማችን አጠራጣሪ የሆኑ ሊንኮች ካጋጠመን ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሚከተሉት አድራሻዎች ማሳወቅ የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
• e-mail: [email protected]
• ነጻ የስልክ መስመር፡ 933
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025