የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በትግራይ ክልል ማይጨው ወረዳ በ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል እየተገነባ ነው

Apr 10, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዝያ 1/2017 (ኢዜአ)፦በትግራይ ክልል ማይጨው ወረዳ በ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የመንግስት በጀት የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል እየተገነባ መሆኑ ተገለጸ።


በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የኤክስቴንሽን አገልግሎት፣ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛ ማእከላት ማጠናከርና ክትትል አስተባባሪ ተክላይ አብርሃ፤የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከላትን እንቅስቃሴና የግንባታ ስራ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።


በማብራሪያቸውም፥ በክልሉ ማይጨው ወረዳ የፌዴራል መንግስት በመደበው 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በጀት ዘመናዊ የሆነ አዲስ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።


የማእከሉ ግንባታ በሶስት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት የሚበቃ ሲሆን ለ15 ሺህ አርሶ አደሮች አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል።


ማእከሉ በዋነኝነት በእርሻ ኤክስቴንሽን፣በእንስሳት ሃብት ልማትና ተዋጽኦ፣በንብ ማነብና በማር ምርት፣በዶሮ እርባታና ሌሎችም መስኮች ስልጠና እንደሚሰጥም አመልክተዋል።


በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ 600 ማእከላትም በመልሶ ግንባታና ግብዓቶችን በማሟላት ወደ አገልግሎት መግባታቸውም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025