የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በምሥራቅ ጎጃም ዞን ከሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማር ለገበያ ቀርበ

Apr 3, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ጎጃም ዞን በበጀት ዓመቱ እስካሁን ድረስ ከሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማር ተመርቶ ለገበያ መቅረቡን የዞኑ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

በጽሕፈት ቤቱ የንብ ሃብት ባለሙያ አቶ ስማቸው ደምሴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እየለማ ያለው ደን ንብ በማነብ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።

በዚህም በያዝነው በጀት ዓመት ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊየን ኪሎ ግራም በላይ ማር ለማምረት ታቅዶ እስካሁን ከሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊየን ኪሎ ግራም በላይ ማምረት መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከግማሽ ሚሊዮን ኪሎ ግራም ማር በላይ ብልጫ አለው ብለዋል።

የማር ምርቱን መሰብሰብ የተቻለውም ከ240 ሺህ በላይ ዘመናዊ፣ ባህላዊና ሽግግር ቀፎዎች ከሚገኘው የንብ መንጋ መሆኑን አስታውቀዋል።

የማር ምርታማነት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ መምጣቱን የገለጹት አቶ ስማቸው፤ ለዚህም የደንና የበጋ መስኖ ልማቱ ንቦች የሚቅስሟቸው የአበባ ዛፎች በስፋት እንዲገኙ በማስቻሉ ነው ብለዋል።

በቀጣይ ሶስት ወራት ውስጥ እቅዱን ሙሉ በሙሉ በማሳካት የአምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሙያዊ እገዛ እየተደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

የአዋበል ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ገድፍ ይታይህ በሰጡት አስተያየት፤ በዚህ ዓመት ከአስር የሽግግርና ዘመናዊ ቀፎ ንብ ከ110 ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ማግኘት ችያለሁ ብለዋል።

ከሶስት የሽግግርና ከስድስት ባህላዊ ቀፎዎች በዓመት ከ60 ኪሎ ግራም በላይ ምርት እያገኙ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአነደድ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ሙሉቀን የቆየ ናቸው።

በዚህ ዓመትም እስካሁን ባለው ከ40 ኪሎ ግራም በላይ ለገበያ አቅርበው ከ25ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን አስረድተዋል።

ከእንስሳትና አሳ ሃብት ተጠሪ ጽሕፈት ቤቱ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፤ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ባለፈው ዓመት ከአንድ ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ለገበያ ቀርቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025