የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የዞኑን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት ይከናወናሉ

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣መጋቢት 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የምዕራብ ኦሞ ዞን ሠላምን አስጠብቆ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎልበቱ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተገለጸ ።


በዞኑ ሠላምና ልማት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ዛሬ በሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕስ መስተዳደረ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤በዞኑ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር ሕዝቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።


በአካባቢው የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል ሕግ የማስከበር ሥራ እንደሚጠናከር ጠቁመው፤ የልማትና የሠላም ግንባታ ሥራዎች ላይ የማኅበረሠቡን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።


ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን መከላከል እንደሚገባ ጠቁመው፤ አመራሩ ዋጋ ከፍሎ የሕዝቡን ሠላም ለማስጠበቅና የልማት ፍላጎት ለማሟላት መትጋት እንዳለበት አስገንዝበዋል።


የአካባቢው ወጣቶች በእርሻና ሌሎች የሥራ ዘርፎች ተደራጅተው በመሠማራት የሥራ እድል ተጠቃሚነታቸውን ማጎልበት እንደሚገባም ጠቁመዋል።


ለዚህም በተለያዩ ምዕራፎች ማኅበረሠቡን ያሳተፈ የምክክር መድረክ በዞኑ ሁሉም መዋቅሮች እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።


የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፥የአካባቢውን ሠላም ለማፅናትና አብሮነትን ለማጠናከር አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል።


የምዕራብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ኬኒ ፤ በምክክሩ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ወደ ተግባር ለመቀየር ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ያሉንን እምቅ ሀብቶች በጋራ አልምተን ሕዝባችንን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት አድርገን እንሰራለን ሲሉም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025