
አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ያዘጋጀው 57ኛው አህጉራዊ የኢኮኖሚ ልማት፣የገንዘብና የፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ በባለሙያዎች ደረጃ ከመጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
“የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን፤ አፈጻጸሙን የሚያልቁ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎችን መቀየስ” የጉባዔው መሪ ሀሳብ ነው።
በጉባዔው የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ፣ ፋይናንስ እና ፕላን ባለሙያዎች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል።

የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ትግበራ የውይይቱ ዋንኛ አጀንዳ ነው።
ባለፉት ቀናት በጉባዔው ላይ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነቱ ስኬታማ ለማድረግ የአፍሪካ ሀገራት፣ የግሉ ዘርፍ እና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ተነስቷል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በጉባዔው ላይ ባደረጉት ንግግር፥ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ በቁርጠኝነት እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
የስምምነቱን ትግበራን ለማፋጠን የጋራ ጥረት ትብብርና ቁርጠኝነት እንደሚጠይቅ አመልክተዋል።
ዲጂታላይዜሽን፣የምግብ ዋስትና እና የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽን ሌሎች የጉባዔው የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው።
በባለሙያዎች ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘው ጉባዔ ዛሬ ይጠናቀቃል። ባለሙያዎቹ ሚኒስትሮቹ የሚወያዩባቸውን አጀንዳዎች ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጉባዔው በሚኒስትሮች ደረጃ መጋቢት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን በጉባዔው መሪ ሀሳብ ላይ ከፍተኛ የፖሊሲ ምክክር መድረክ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም ከጉባዔው ጋር የተጓዳኙ የተለያዩ ሁነቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚደረጉም ኢዜአ ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025