
አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ተቋማትን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትና ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ISO 21001/2018 ለመተግበርና የሙያ ብቃት ምዘና እና ሰርተፊኬሽን ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በመታገዝ አውቶሜት ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው ላይ ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የብቃት ምዘና ማረጋገጫ ማዕከላትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኮሌጆች ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ተቋማትን ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስቴሩ ባለፉት ሁለት ዓመታት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር ባከናወነው ስራ ውጤቶች መገኘታቸውን አመልክተዋል።
በዚህም ለሌሎች ምሳሌ መሆን የሚችሉ ተቋማት መፈጠራቸውንና አዳዲስ ተቋማት ከቀድሞዎቹ ልምድ በመውሰድ ራሳቸውን የማሻሻል ስራ እያከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው ተቋማት የጥራት ሥራ አመራር ስርዓቱን በሚጠበቀው ደረጃ ለመተግበር አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባቸው ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025