የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያን በአፍሪካ ምቹ የቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ያላት አገር ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

Mar 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን በአፍሪካ ምቹ የቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ያላት አገር ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለፀ።

ሦስተኛው ዙር የአፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮንሽፕ 2025 ውድድር በሳይንስ ሙዚየም ተጀምሯል።

በውድድሩ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተማሪዎች የሚወዳደሩ ሲሆን በኢትዮጵያ ባሉ ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ አፍሪካውያን ተማሪዎችም ተሳትፈውበታል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ኢትዮጵያ ዘላቂና ቀጣይነት ያለው እድገት ለማስመዝገብ እንዲሁም ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሰራች ነው።


የተለያዩ የህግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት በዲጂታል ዘርፍ ምቹ ምህዳር ለመፍጠር መሰራቱን አንስተው ይህም በዘርፉ ያለውን ክህሎትና እውቀት ለማዳበርና የፈጠራ ሃሳብን ለማበርከት ማገዙን ጠቁመዋል።

የቴክኖሎጂን ተደራሽነት፣ አካታችነትና ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በዘርፉ ከምስራቅ አፍሪካ ብሎም ከአፍሪካ ምቹ ስነምህዳር ያላት አገር ለማድረግ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል ብለዋል።

ከአለም አቀፍ መስፈርትና ከአገሪቱ መሪ የልማት እቅድ ጋር የተናበበ ምቹ ስነምህዳር ለመፍጠር የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎች መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል።

በዘርፉ ያሉ ተዋናዮችን በማሳደግ ያሉ ሀብትና እውቀትን በማልማት ኢትዮጵያን የሚያስጠሩ ዜጎች ለማፍራት የሚያስችል ስራ ተሰርቷል ብለዋል።

የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ለዲጂታል ክህሎት ልማት አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

የዲጂታል መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እና የግሉ ዘርፍ ለዲጂታል ልማት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ የሚያስችል ምህዳር መፈጠሩን ተናግረዋል።

ለሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ሂሳብና ምህንድስና ትኩረት በመስጠት ከትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።

የአፍሪካ ሮቦቲክስ ውድድር ፈጠራን የሚደግፉ ስራዎች የሚታዩበት እንደሆነና ሃሳብን በማልማትና በማሳደግ እንዲሁም ወደተግባር በመለወጥ ሀብትና የስራ እድል እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

የኢትዮ ሮቦቲክስ ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰናክሬም መኮንን በበኩላቸው፤ ውድድሩ የተማሪዎችን የፕሮግራሚንግ፣ ዲዛይን፣ ምህንድስና እና ተዛማጅ ክህሎቶቻቸውን እንዲያሻሽሉ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

ማዕከሉ በዘርፉ ስራዎችን ሲያከናውን 15 አመት ማስቆጠሩን ገልፀው እስካሁን ባለው ተወዳዳሪዎች ከአገር ውስጥ ባለፈ በተለያዩ የአለም አገራት ኢትዮጵያን በመወከል መወዳደር ችለዋል ብለዋል።

ውድድሩ አገራዊ አበርክቶው ከፍ እንዲል ከመንግሥት ጋር በትብብር እየሰራን ነው ያሉት ሥራ አስኪያጁ በቀጣይም ውድድሩን በአፍሪካ ደረጃ ለማስፋት ግብ ይዘናል ለዚህም አስፈላጊው ድጋፍ እንሻለን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በውድድሩ የተሳተፉት ዊዳድ አብደላና ማቲያስ ዮናስ በሮቦቲክስ ዘርፍ ከአገር ውስጥ አልፈው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳድረው አገራቸውን ማስጠራት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025