
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፦ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩባቸውን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ከአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ እና ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አመራሮች ጋር በመሆን በስልጠና ላይ የሚገኙ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች (ስታርትአፖችን) ጎብኝተዋል።
ዶክተር አህመዲን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ቴክኖሎጂ የሥራ ፈጠራና ክህሎት ለውጥ መሪ ቁልፍ በመሆኑ ዘርፉን ማበረታታት፣ የወጣቶችን ዕምቅ ችሎታ ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን አመቺ ሁኔታን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብለዋል።
እየተሰጠ ያለው ስልጠናም የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ የሚያጠናክርና ተጨማሪ አቅም የሚፈጥርላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

በኢንስቲትዩቱ የሚገኘውን ሜከርስፔስ (BiTec) የሚገኙ ከሀሳብ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡ የተለያዩ ችግር ፈች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መጎብኘታቸውን አመልክተዋል።
ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩበትን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የገለጹት ዶክተር አህመዲን፤ በስልጠናው ከፍተኛ ሚና ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦችን አመስግነዋል።
ለስታርትኦፕች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል በመልዕክታቸው።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025