
አዳማ፤የካቲት 10/2017 (ኢዜአ).፦የዋጋ ግሽበትን የመቆጣጠርና የመረጃ ትንተና ስርአትን ማሻሻል እንደሚገባ ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከመላ ሀገሪቷ ለተውጣጡ የመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች በአዳማ ስልጠና ሰጥቷል።

በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍሰሐፅዮን፥ በኢኮኖሚ እድገትና ልማት ሂደት የዋጋ ግሽበት ቁጥጥርና ትንተና መረጃ አቅርቦትን ማሻሻል ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ የሚደረጉ ጥናቶች ለፖሊሲ ትልቅ ግብአት መሆናቸውን አንስተው፥ መረጃን በተሟላ መልኩ በጥራት መሰብሰብ እንደሚገባ እና የመረጃ ሰብሳቢዎች እውቀትና ክህሎት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
የገቢ ግብርን ከመወሰንና ሌሎችም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ተግባራትን ለማከናወን አስፈላጊነቱን አብራርተው በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር)፤ የችርቻሮ የዋጋ ጥናት ለፖሊሲ ቀረፃና ውሳኔ ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ለአገልግሎቱ በልዩ ትኩረት የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም መረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ጥራት ያለው መረጃ ለመሰብሰብ በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአዳማ ከዛሬ ጀምሮ ለ20 ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የተውጣጡ 200 መረጃ ሰብሳቢዎች እና ተቆጣጣሪዎች እየተሳተፉ ነው።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025