🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ግብዓትና ምርት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ በገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔ ተላለፈ።
ሚኒስቴሩ ይህንን የፈቀደው የንግድ ቀጠናዎቹ ባለሀብቶችን ይበልጥ የሚስቡ እንዲሆኑ ለማድረግ መሆኑን ገልጿል።
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት በሚፈለገው መጠን እንዳያድግ ምክንያት ከሆኑት መካከል የካፒታል እጥረት፣ የግብዓት አቅርቦት ችግር እና የባለሙያ እጥረት በዋነኛነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ በመረጃው ጠቁሟል።
በመሆኑም እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ በማቃለል የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ልማትን ማሳደግ እንደሚገባ አስታውቋል።
በዚህም መሠረት ግብዓቶች እና ሌሎችም ምርቶች በበቂ መጠን ለገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ፣ አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ እና ታክስ ውስን በሆነው ካፒታላቸው ላይ የሚያሳድረውን ጫና ማቃለል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
በነዚህ ምክንያቶች አስመጪዎች ግብዓቶችን እና ምርቶችን ቀረጥና ታክስ ሳይከፍሉ ወደ አገር አስገብተው፣ ለግብዓቱ ወይም ለምርቱ ገበያ ባገኙ ጊዜ ቀረጥና ታክሱን የሚከፍሉበትን አሰራር የሚፈቅድ የነፃ የንግድ ቀጣና አሰራር ተዘርግቷል።
ይህንን ሥርዓት የሚያስፈጸሙ ነፃ የንግድ ቀጣናዎችም በየአካባቢው የተቋቋሙ መሆኑ ተመልክቷል።
ይህንን ተከትሎም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ተሰማርተው ምርትና ግብዓት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከላይ ከተጠቀሰው የታክስ አከፋፈል ስርዓት በተጨማሪ ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደርጓል።
በመሆኑም ባለሀብቶች ይህንን ዕድል በመጠቀም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ እንዲሰማሩ የገንዘብ ሚኒስቴር ጥሪውን አስተላልፏል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025