የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ለተሰማሩ ባለሀብቶች የገቢ ግብር ዕፎይታ ተፈቀደ

Apr 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ግብዓትና ምርት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ በገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔ ተላለፈ።

ሚኒስቴሩ ይህንን የፈቀደው የንግድ ቀጠናዎቹ ባለሀብቶችን ይበልጥ የሚስቡ እንዲሆኑ ለማድረግ መሆኑን ገልጿል።

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት በሚፈለገው መጠን እንዳያድግ ምክንያት ከሆኑት መካከል የካፒታል እጥረት፣ የግብዓት አቅርቦት ችግር እና የባለሙያ እጥረት በዋነኛነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ በመረጃው ጠቁሟል።

በመሆኑም እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ በማቃለል የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ልማትን ማሳደግ እንደሚገባ አስታውቋል።

በዚህም መሠረት ግብዓቶች እና ሌሎችም ምርቶች በበቂ መጠን ለገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ፣ አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ እና ታክስ ውስን በሆነው ካፒታላቸው ላይ የሚያሳድረውን ጫና ማቃለል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

በነዚህ ምክንያቶች አስመጪዎች ግብዓቶችን እና ምርቶችን ቀረጥና ታክስ ሳይከፍሉ ወደ አገር አስገብተው፣ ለግብዓቱ ወይም ለምርቱ ገበያ ባገኙ ጊዜ ቀረጥና ታክሱን የሚከፍሉበትን አሰራር የሚፈቅድ የነፃ የንግድ ቀጣና አሰራር ተዘርግቷል።

ይህንን ሥርዓት የሚያስፈጸሙ ነፃ የንግድ ቀጣናዎችም በየአካባቢው የተቋቋሙ መሆኑ ተመልክቷል።

ይህንን ተከትሎም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ተሰማርተው ምርትና ግብዓት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከላይ ከተጠቀሰው የታክስ አከፋፈል ስርዓት በተጨማሪ ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደርጓል።

በመሆኑም ባለሀብቶች ይህንን ዕድል በመጠቀም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ እንዲሰማሩ የገንዘብ ሚኒስቴር ጥሪውን አስተላልፏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025