የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ከሀዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች ከ45 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል

Jul 30, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ ከላካቸው ምርቶች ከ45 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱን አስታወቀ።


የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቲዮስ አሸናፊ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ከዚህ ቀደም በጨርቃ ጨርቅ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል።


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን መሆኑን ተከትሎ በተለያዩ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸው ባለሀብቶች ወደልዩ ዞኑ ለመግባት ስምምነት እየፈረሙ መሆኑን ገልጸዋል።


በተለይ የምስራቅ እስያ ካምፓኒዎች በብዛት እየገቡ እንደሚገኙ ጠቁመው፣ከእነዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ በሶላር ምርት ዕውቅና ያላቸው እንደ ቶዮ ሶላር፣ ካናዳ ሶላር እና ኦርጂን ሶላር የመሳሰሉ ካምፓኒዎች ፋብሪካቸውን ተክለው ወደምርት ሂደት መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡


ይህም ከፍተኛ የሆነ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር፣የሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም የወጪ ምርት መጠን እንዲጨምር እና ገቢም እንዲያድግ ማድረጉን ተናግረዋል።


የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ወደ ተለያዩ ሀገራት ከላካቸው ምርቶች ከ45 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱንም አቶ ማቲዮስ አንስተዋል፡፡


ገቢው የተገኘው ወደ አውሮፓ፣ሰሜን አሜርካ፣ እስያና አፍርካ ውስጥ በሚገኙ 14 የገበያ መዳረሻዎች ከተላኩ ምርቶች መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በሀዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከዚህ ቀደም ሥራ ላይ ከነበሩ ኩባንያዎች በተጨማሪ የተለያዩ ኩባንያዎች ስምምነት ፈርመው ወደ ምርት ሂደት መግባታቸው ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.