የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የ2018 በጀት ዓመት የማንሰራራት ጉዟችንን የሚያፀኑ አዳዲስ እመርታዎችን ለማስመዝገብ በጋራ የምንተጋበት ዓመት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Jul 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017(ኢዜአ)፦ የ2018 በጀት ዓመት የማንሰራራት ጉዟችንን የሚያፀኑ አዳዲስ እመርታዎችን ለማስመዝገብ በጋራ የምንተጋበት ዓመት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገተለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን እንደመነሻ በመውሰድ በተዘጋጀው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት እየተካሄደበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የ2017 በጀት ዓመት በብዙ መልኩ የኢትዮጵያ የብልጽግና ታሪክ እጥፋት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዓመቱ እውነትም የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን መነሻ የሆነ ዓመት ነበር ብለዋል።


የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድም እነዚህን መልካም አፈጻጸሞች መነሻ የሚያደርግ መሆኑንም ገልጸዋል።

በበጀት አመቱ በኢኮኖሚው ዘርፍ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማድረግ የከረሙ ስብራቶቻችን ጠግነናል ሲሉም አክለዋል፡፡

የሕዳሴ ግድብን አጠናቅቀናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጋዝ ፕሮጀክታችንንም እያጠናቀቅን እንገኛለን ነው ያሉት፡፡

በከተሞቻችን የጀመርናቸው የኮሪደር ልማቶች ውጤት ማምጣት ጀምረዋል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የገጠር ኮሪደርም ጀምረናል ሲሉ ገልጸዋል።

የ2018 በጀት ዓመት ግቦቻችን እነዚህን መልካም አፈጻጸሞች መነሻ የሚያደርጉ፣ ካለፈው በላይ ትጋትና ጥረት የሚጠይቁ ናቸው ሲሉም አስገንዝበዋል።

ለብቻ መሮጥን ብቻ ሳይሆን ጠንካራ ቅንጅትንም ይፈልጋሉ ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ዛሬ በእኛ እጅ ናት ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዲሱ በጀት ዓመት የላቁ ድሎችን በማስመዝገብ የኢትዮጵያን ማንሠራራት የሚያውጀው ትውልድ አካል እንደሆንን በማመን ለበለጠ ስኬት በትጋት መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.