አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017(ኢዜአ)፦ የ2018 በጀት ዓመት የማንሰራራት ጉዟችንን የሚያፀኑ አዳዲስ እመርታዎችን ለማስመዝገብ በጋራ የምንተጋበት ዓመት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገተለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን እንደመነሻ በመውሰድ በተዘጋጀው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት እየተካሄደበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የ2017 በጀት ዓመት በብዙ መልኩ የኢትዮጵያ የብልጽግና ታሪክ እጥፋት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዓመቱ እውነትም የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን መነሻ የሆነ ዓመት ነበር ብለዋል።
የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድም እነዚህን መልካም አፈጻጸሞች መነሻ የሚያደርግ መሆኑንም ገልጸዋል።
በበጀት አመቱ በኢኮኖሚው ዘርፍ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማድረግ የከረሙ ስብራቶቻችን ጠግነናል ሲሉም አክለዋል፡፡
የሕዳሴ ግድብን አጠናቅቀናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጋዝ ፕሮጀክታችንንም እያጠናቀቅን እንገኛለን ነው ያሉት፡፡
በከተሞቻችን የጀመርናቸው የኮሪደር ልማቶች ውጤት ማምጣት ጀምረዋል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የገጠር ኮሪደርም ጀምረናል ሲሉ ገልጸዋል።
የ2018 በጀት ዓመት ግቦቻችን እነዚህን መልካም አፈጻጸሞች መነሻ የሚያደርጉ፣ ካለፈው በላይ ትጋትና ጥረት የሚጠይቁ ናቸው ሲሉም አስገንዝበዋል።
ለብቻ መሮጥን ብቻ ሳይሆን ጠንካራ ቅንጅትንም ይፈልጋሉ ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬ በእኛ እጅ ናት ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዲሱ በጀት ዓመት የላቁ ድሎችን በማስመዝገብ የኢትዮጵያን ማንሠራራት የሚያውጀው ትውልድ አካል እንደሆንን በማመን ለበለጠ ስኬት በትጋት መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025