የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በመዲናዋ ቀልጣፋ የፍትሕ አገልግሎትን ተደራሽ የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ ቀልጣፋ የፍትሕ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን የተለያዩ ውሳኔዎችና ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ አበባ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንት ተስፋዬ መለሰ የፍርድ ቤቶችን የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

በበጀት ዓመቱ ፍርድ ቤቶች ለሚቀርቡላቸው ጉዳዮች ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

የፍርድ ቤት የአገልግሎት ቅልጥፍና መለኪያዎች የመዛግብት ማጣራት ምጣኔና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ውሳኔ መስጠት መሆኑን በሪፖርታቸው አመላክተዋል።

በ2017 በጀት ዓመት የመዛግብት የማጣራት ምጣኔን 97 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ በሁሉም ፍርድ ቤቶች መሰራቱን አብራርተዋል።

ከ2016 በጀት ዓመት የዞሩና በ2017 አዲስ የተከፈቱትን ጨምሮ ከአጠቃላይ 162ሺህ 97 መዛግብት ውስጥ 159 ሺህ 65ቱ እልባት አግኝተዋል ብለዋል።

ዓመታዊ የመዛግብት የማጣራት ምጣኔውም 98 በመቶ መፈጸሙን ነው ያነሱት።

የዳኝነት ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ዳኞች ስራቸውን ሲያከናውኑ ከፈጻሚው አካል፣ ከፍርድ ቤት አመራሮችና ከጎንዮሽ ተጽእኖ ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲያገለግሉ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በፍርድ ቤቶች የአገልግሎት አሰጣጥን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግና የተገልጋይ እርካታን ለመጨመር የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

የፍርድ ቤት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ መደገፍ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት መስጠት ብልሹ ስነ-ምግባር የታየባቸው ሰራተኞችና ዳኞች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፍርድ ቤቶችን ማጠናከር የዜጎችን መብት ለማስጠበቅና ህጎችን በትክክል በመተግበር የፍትሕ አገልግሎት ውጤታማነትን ለመጨመር ያግዛል ብለዋል።

ልማትን ለማፋጠን፣ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ፍትሃዊነት ለማስፈን በፍርድ ቤቶች የተጀመሩ ሪፎርሞችን ማጠናከር እንደሚገባም ነው አፅንኦት የሰጡት።

ከተማ አስተዳደሩም ለፍርድ ቤቶች አስፈላጊውን መሰረተ ልማት በማሟላት ግልጽ እና ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን እውን ለማድረግ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ከንቲባዋ አረጋግጠዋል።

የምክር ቤት አባላት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ያነሷቸው አስተያየቶች በግብዓትነት በመውሰድና ለጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ሪፖርቱ ጸድቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025