የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>በሰሜን ወሎ ዞን በጋዞ ወረዳ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመረቁ</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ የካቲት 09/2017 (ኢዜአ) በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ጋዞ ወረዳ በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ።

ከተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች ውስጥም የአስተዳደር ምክር ቤት ህንፃን ጨምሮ ሶስት ጤና ጣቢያዎች፣ ስምንት የትምህርት ቤት ማሻሻያና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ይገኝበታል።

በተጨማሪም ሰባት ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ፣ አነስተኛ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት፣ የመስኖ ካናል ፣ ሁለት የእንስሳት ጤና ኬላና የእንስሳት ዝርያ ብዜት ማዕከላትና ሌሎችም ይገኙበታል።

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በምረቃ ስነ-ስርዓ ላይ እንደገለጹት የተገነቡት የልማት ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ናቸው።


ፕሮጀክቶቹን ጠብቆ ለረጅም ጊዜ ለመጠቀምና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር የልማት መሠረት የሆነውን ሠላም ማጽናት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው የተመረቁትና በጉብኝት የታዩት የልማት ፕሮጀክቶች በአመራሩና በህዝቡ ቁርጠኝነት የተከናወኑ ናቸው ብለዋል።

አሁንም ሠላምን ይበልጥ በማጽናት የህዝብን ተጠቃሚነት በምናረጋግጥበት ልማት ላይ ይበልጥ መስራት ይገባል ሲሉም አክለዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አራጌ ይመር በበኩላቸው በዞኑ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በቀጣይም አሁን የሚታየውን የተሻለ ሠላም ይበልጥ በዘላቂነት በማረጋገጥ የዞናችንን ልማት ለማፋጠን በቁርጠኝነት ከህብረተሰቡ ጋር በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

በምረቃ ስነ- ስርዓቱ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የአመራር አባላት እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025