የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።

በከተሞቹ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን አስተማማኝ ለማድረግ የዲስትሪቡሽን መስመር መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት በመከናወን ላይ ይገኛል።

ፕሮጀክቱ የኃይል ማከፋፈያ ኔትወርክ ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዙ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚወጡ መስመሮችን መልሶ መገንባትና ማሻሻል፤ እንዲሁም ከፈቃድ በላይ የሆነ የኃይል ፍጆታን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ 62 የሎድ ብሬክ ስዊቾችን መግጠምን ያካትታል።

የሚገነቡት መስመሮች በኮንክሪት ምሰሶዎች እና በሽፍን ኬብል የሚከናወኑ በመሆናቸው ለአደጋ የማይጋለጡና ለረጅም ዓመታት አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ናቸው ተብሏል።

የአዲስ አበባ ዲስትሪቢውሽን ሪሃቢሊቴሽን 4ኛ ምዕራፍ ፕሮጀክት ሃላፊ ቅድስት ላቀው ለኢዜአ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ በዋናነት የኃይል ኔትወርክ እድሳትን እና የመስመሮችን አስተማማኝነት ማረጋገጥን ዓላማ ያደረገ ነው።

በዚህም 2 ሺህ አዲስ የተለያየ አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተከላና 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮች አቅም የማሳደግ ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል፡፡

በፊዩዝ የነበረ ትራንስፎርመር ወጪ በዲስትሪቢዩሽን ቦክስ እንደሚሆን ተናግረው ይህም የሚቆራረጡ መስመሮች በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች 673 ኪሎሜትር የሚሆን መስመሮች እንደሚቀየሩ ገልጸው፤ ሽፋን የሌለው የኤሌክትሪክ መስመር ገመዶች እንደሚቀየሩና የኤሌክትሪክ መቆራረጥን እንደሚያስቀር ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ አስተማማኝ የሀይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።


የቻይና ኢነርጂ ግሩፕ ምክትል ማናጀር ሁ ዊሚንግ ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን የማቆም ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ የማገናኘት እና የሙከራ ስራ መሆኑን ጠቁመዋል።


በፕሮጀክቱ የሎት አንድ ሳይት መሀንዲስ አረአያ ጌታሁን በምስራቅ ሪጅን ካሉ ሳይቶች ውስጥ ሶስቱ መጠናቀቃቸውን ገልጸው፤ በተያዘለት ጊዜ ማጠናቀቅ የሚያስችል ስራም እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026