🔇Unmute
ገንዳውኃ፣ መጋቢት18/2018 (ኢዜአ):-በምዕራብ ጎንደር ዞን በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 80 በርሜል ነዳጅ ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡
ነዳጁን መያዝ የተቻለው በምእራብ አርማጭሆ ወረዳ በሁለት አይሱዙ ተሽከርካሪ ተጭኖ በመጓጓዝ ላይ እያለ ነው።
በዚህም ፖሊስ 80 በርሜል ነዳጅ ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም በአቋራጭ ለመክበርና ለህገ ወጥ ዓላማ ለማዋል በማለም በሀገርና ህዝብ ላይ ተጨማሪ ጫና ለመፍጠር የተሞከረ ህገወጥ ተግባር መሆኑን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ምስጋናው ካሴ አብራርተዋል።
እንደዚህ አይነት ወንጀሎችን ለመከላከል የፀጥታ አካላት ባደረጉት ጠንካራ ፍተሻና በህብረተሰቡ ጥቆማ መሰረት በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረው ነዳጅ መያዙን ተናግረዋል።
#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026