የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በዞኑ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያን ማረጋጋት ተችሏል

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን ማረጋጋት መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

በክልሉ የዋጋ ንረትን ለማርገብ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ለሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበራት ለምርት አቅርቦት እንዲሆን በመንግስት 208 ሚሊዮን ብር መመደቡ ምርቶችን በተሻለ ለማቅረብ አስተዋጽኦ ማድረጉም ተመልክቷል።

የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ ተወካይ ፈጠነ ሞገስ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በዞኑ የሚገኙ 41 የሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበራት ከአርሶ አደሩ ጋር ትስስር በመፍጠር የግብርና ምርት ካለበት አካባቢ በማምጣት እጥረት ወደ ሚስተዋልበት የማቅረብ ሥራ እያከናወኑ ይገኛሉ።

በዚህም አርሶ አደሮች ምርታቸውን በግብይት ማዕከላት አቅርበው ከመሸጥ ባለፈ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በቅርበት ለመግዛት መቻላቸውን ጠቁመዋል።

እንደ ፈጠነ (ዶ/ር) ገለጻ፤ ባለፉት 8 ወራት 470 ሺህ ኩንታል የግብርና እና 82ሺህ ኩንታል የኢንዱስትሪ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማህበረሰቡ በማቅረብ ገበያን የማረጋጋት ሥራ ተከናውኗል።

ለምርት አቅርቦቱ ከመንግስት ለህብረት ሥራ ማህበራት የተመደበው 208 ሚሊዮን ብርም ጤፍ፣ ስንዴ፣ ስኳር፣ የዳቦ ዱቄት፣ ዘይትና ሌሎች የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አግዟል ብለዋል።

ፈጠነ (ዶ/ር) አክለው እንደገለጹት፣ በዘንድሮው የበጋ ወቅት በተካሄደ የመስኖ ልማት የተሳተፉ አርሶ አደሮች የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ በቂ ምርት ለገበያ እንዲቀርብ እያገዙ ነው።

ይህም ህብረተሰቡ ከኢድ አል ፈጥር በዓል በተጨማሪ መጪውን የትንሳኤ በዓል የሚፈልገውን የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።

በሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ የመስኖ አግሮኖሚስት ባለሙያ አቶ ዘሩ ገረመው በበኩላቸው እንዳሉት፤በመኸር እና በበጋ መስኖ የሰብል ልማት ምርታማነት ማደግ በቂ ምርት ወደ ገበያው ለማቅረብ አስችሏል።

በተያዘው የበጋ ወቅት እየተካሄደ ባለው የመስኖ ልማትም ስንዴና ከ600 ሺህ ኩንታል በላይ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት በማምረት ለገበያ እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህም የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር በማድረግ ሲስተዋል የነበረውን የዋጋ ንረት ለማርገብ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረጉን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026