🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ለ2018/2019 የምርት ዘመን የሚውል ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ዘመናዊ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ ገብቶ ለአርሶ አደሮች እየተሰራጨ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው የግብዓት አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ ኃይለኢየሱስ ዳምጤ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዞኑ ትርፍ አምራች በመሆኑ ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦቱ ቀድሞ እንዲከናወን እየተደረገ ነው።
በዚህም ለመጪው የምርት ዘመን በአጠቃላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ ሥራዎች ተጀምረዋል።
እስካሁን በተደረገው ጥረትም ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ የገባ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በመሠረታዊ ማኅበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል።
ይህም በምርት ዘመኑ በእቅድ የተያዘውን 25 ሚሊዮን ኩንታል የምርት ግብ ለማሳካት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026