🔇Unmute
አሶሳ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግልገል በለስ ከተማ የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ተናገሩ።
የኮሪደር ልማት ከተሞችን ከማዘመን ባለፈ ለኑሮና ለንግድ አመቺ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።

ልማቱ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በመላ የሀገሪቱ ከተሞች በመስፋት የከተሞቹን ገጽታ በእጅጉ እየለወጠ ይገኛል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማን ጨምሮ በባምባሲ እና ግልገል በለስ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ግልገል በለስ ከተማ 3 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ከተጀመረ ሁለት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ለኢዜአ ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለነዋሪዎቿ እና ለጎብኚዎች ተመራጭ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
ከተማዋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መዳረሻ በመሆኗ የኮሪደር ልማቱ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን አካቶ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።
የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የህዝብ መጸዳጃ ቤት፣ ካፍቴሪያና የመዝናኛ ማዕከላትን የያዘው የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
አሁኑ ላይ የእግረኞች እና የብስክሌት መንገድ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነና የአገልግሎት መስጫ ማዕከላቱንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች የኮሪደር ልማቱን በጉልበት እና በገንዘብ መደገፋቸውን ጠቁመው፤ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ከንቲባው ጠይቀዋል።
የኮሪደር ልማቱ በፍጥነት እና በጥራት እንዲከናወን አመራሩ የቅርብ ክትትል እያደረገ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026