የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋ የቴሌኮም እና የባንክ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋ የቴሌኮም እና የባንክ አገልግሎቶችን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ኢትዮ- ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቁ።

38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 8 እና 9/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።


ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው ኢትዮ-ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለህብረቱ ጉባኤ ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል።

የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ኮሙኒኬሽን ኦፊሰር መሳይ ውብሽት፤ እንግዶች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከመድረሳቸው ጀምሮ የቴሌኮም አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ በቂ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።

በሚያርፉባቸው ሆቴሎችና በህብረቱ ዋና መስሪያ ቤትም የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በማቋቋም የሲም ካርድና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በቀላሉ የሚያገኙበት ሥርዓት ከወዲሁ መዘርጋቱን ተናግረዋል።


የኢትዮ-ቴሌኮም የአገልግሎቶች ማረጋገጫ ቺፍ ኦፊሰር አበበ ያንባው፤ በህብረቱ ጉባኤ ለመታደም የሚመጡ እንግዶች በቆይታቸው ከኔትወርክ ጋር የተያያዘ የቴክኒክ ችግር እንዳያጋጥማቸው በቂ ዝግጅት አድርገናል ብለዋል።

ለዚህም አስተማማኝ የ4 ጂ እና 5 ጂ ኔትወርክ በጥራት እንዲያገኙ በዋና ዋና ማዕከላት ማሻሻያ ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።

የአገልግሎት መቋረጥ እንዳይፈጠር አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ የባለሙያ ስምሪት መሰጠቱን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል እንግዶች በቆይታቸው ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገልጿል።

በባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ ዲቪዥን መርቻንትና ኤጀንት ማኔጅመንት ዳይሬክተር ብሌን ኃይለ ሚካኤል፤ የሚያስፈልጋቸውን የውጭ ምንዛሬ እንዲፈጽሙ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።


ከዚህ በተጨማሪ በሆቴሎችም የፖስ እና ሌሎች የዲጂታል ባንኪንግ አማራጮችን በመጠቀም ግብይትና ክፍያ የሚፈጽሙበት ዕድል መፈጠሩን ነው ያነሱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026