የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት ለገበያ ለማቅረብ እየተሠራ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በተያዘው የበጀት ዓመት 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየሠራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ወልያብ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በክልሉ የድንጋይ ከሰል ሀብት በስፋት መኖሩን አንስተዋል።


በአሁኑ ወቅትም በዳውሮ እና ኮንታ ዞኖች የድንጋይ ከሰል የማምረት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በአጠቃላይ እንደ ክልል ያለውን የድንጋይ ከሰል መጠን በጥናት ለመለየት እየተሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

በ2018 የበጀት ዓመት 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት በማዕከላዊ ገበያ በኩል ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ለማቅረብ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።


በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሦስት ወራት 82 ሺህ ቶን ማምረት መቻሉንም አስረድተዋል።

በማዕድን ዘርፉ በተያዘው የበጀት ዓመት እስካሁን ባለው ሂደት ለ1 ሺህ 499 ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026