የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ የሆነ የባቡር አካዳሚ ልትገነባ ነው  

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ የሆነ የባቡር አካዳሚ ልትገነባ ነው።

አካዳሚው የሚገነባው በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ ሲሆን፤ ግንባታው በ62 ሄክታር መሬት ላይ ያርፋል።


የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው፤ በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ከሁሉም አጎራባች ሀገሮች ጋር የሚያስተሳስሩ ዘመናዊ የባቡር መሠረተ ልማቶችን ከመዘርጋት ጎን ለጎን ኢንዱስትሪውን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስትራቴጂ ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።


ለባቡር ኢንዱስትሪው የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት ተተኪ ባለሙያዎችን የማሰልጠን ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የሚገነባው የባቡር አካዳሚ ግንባታው ሲጠናቀቅ የኢንዱስትሪውን ተደራሽነት ለማስፋት እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ለአጎራባች አገራት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን በመስጠት የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ እንደሚያገለግልም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው በበኩላቸው፤ የባቡር ትራንስፖርት የወጪ እና ገቢ ምርቶችን እንቅስቃሴን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳልጥ ተናግረዋል።


አካዳሚው ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ቀጣናውን በትምህርት ዲፕሎማሲ እንደሚያስተሳስር ተናግረዋል።

የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ እንደገለጹት፤ አካዳሚው ለከተማዋ በረከትና ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ ሆኖ ያገለግላል።

በመሆኑም አካዳሚው በተቀመጠለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026